Skip to main content
በዶ/ር ቦጋለች  ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል CPD Center ለተከታታይ 03 ቀናት ከ14-16/04/2018 ዓ/ም ሲሰጥ የቆየዉ Oxygen Supply Chain Management ሥልጠና መጠናቀቁ ተገለፀ፡፡

በመርሃ-ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የመድኃኒትና ህክምና መገልገያ መሣርያዎች ዳይሬከረቶሬት የፋርማሲ አገልግሎት ኬዝ-ቲም ቡድን መሪ የሆኑት አቶ መኅቡብ ኑሪ የመክፈቻ ንግግር በማድረግ የሥልጠናዉ ዓላማ እና ግብ ላይ ያተኮረ ቁልፍ መልዕክት በማስቀመጥ ሥልጠናዉን ባይፋ አስጀምረዋል፡፡

በሥልጠናዉላይ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሁሉም ዞን ጤና መምሪያ፤ ልዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት እና ሆስፒታሎች  የተወጣጡ የፋርማሲ አስተባባሪዎች፤ባዮሜድካል  እንጅኔሮች/ቴክኒሽያኖች እና ሌሎች ጤና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል ።

ሥልጠናዉስታንዳርዱን በጠበቀ መልኩ መካሄዱን የCPD Center አስተባባሪ የሆኑት አቶ ዘላለም በቀለ ገልፀዋል፡፡

ዶ/ር ቦጋለች  ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል CPD Center

ዱራሜ፤ ታህሳስ 17/2018 ዓ/ም